ዩኒቨርሲቲዎች ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞችን ዛሬ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም መቀበል ጀምረዋል፡፡

የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል።

በወጣው መርሐግብር መሰረት ሰኞ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ይጀምራል፡፡

ፈተናውን ለመውሰድ 608 ሺህ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ 150 ሺህ የሚሆኑት በበይነ መረብ የሚፈተኑ ናቸው።

ምስል፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

EthioNews #Ethiopia